የኢራን አምባሳደር አሜሪካ በቀጣይ ድርድሮች ተጨባጭ አቋም መያዝ አለባት አሉ
ጄኔቫ ውስጥ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢራን አምባሳደር ሆኑት አሊ ባህሬኒ በቴህራን እና ዋሽንግተን መካከል የሚደረጉ ድርድሮች እንዲቀጥሉ የሚፈለግ ከሆነ አሜሪካ ወደ ኢራን ወደቦች የሚደረጉ ጉዞዎች ላይ የጣለችውን እገዳ ማብቃት እንዳለበት ተናገሩ።
ከቢቢሲ ጋር ቃለ መጠይቅ ያደረጉት አምባሳደሩ፤ አሜሪካ ጣለችው እገዳ “ከፍተኛ” የተኩስ አቁም “ጥሰት” መሆኑን ገልጸዋል።
በድጋሚ ድርድር ውስጥ በሚገባበት ወቅት “አሜሪካ ለኢራን መብቶች እና ለኢራን ምክንያታዊ ጥያቄዎች እውቅና በመስጠት ተጨባጭ አካሄድ ልትከተል” እንደሚገባ ተናግረዋል።
ቴህራን ድርድር የምታደርገው “ሌላኛው ወገን ኢራንን ለማጥቃት ተጨማሪ ዝግጅት” የሚያደርግበት ዕድል ለመስጠት እንዳልሆነም አክለዋል።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ወታደሮች ትዕዛዝ የሚሰጣቸው ከሆነ በድጋሚ ዘመቻ ለመክፈት ዝግጁ መሆናቸውን ከዚህ ቀደም ተናግረው ነበር።
አምባሳደሩ ከቢቢሲ ጋር ባደረጉት ቆይታ ቀጣይ እርምጃ ምን መሆን አለበት የሚለውን በተመለከተ በኢራን ከፍተኛ አመራሮች መካከል ክፍፍል ተፈጥሯል መባሉን ውድቅ አድርገዋል። ይልቁንም ችግር የሆነችው “ሙሉ ተቃርኖ” እና ክፍፍል ውስጥ ያለችው አሜሪካ መሆኗን ተናግረዋል።