በኢትዮጵያ በቫይረሱ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው 55 ሰዎች ከማህበረሰቡ ተገኙ

በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ከተከሰተ ጀምሮ ከፍተኛ የተባለው፣ 88 ሰዎች ሰዎች በዛሬው ዕለት በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። በቫይረሱ ከተያዙት 55ቱ የውጭ ሃገር ጉዞም ሆነ ከህመምተኛ ጋር የታወቀ ንክኪ መኖሩ አለመታወቁ ብዙዎችን አስደንግጧል፤ ይህም ሁኔታ የኮሮናቫይረስ በማህበረሰቡ ውስጥ እየተዛመተ ስለመሆኑ ጠቋሚ ነው ተብሏል። ከነዚህም መካከል 73ቱ ሰዎች በአሁኑ ወቅት በሃገሪቱ የቫይረሱ የስርጭት ማዕከል ከሆነችው ከአዲስ አበባ ናቸው። በአጠቃላይ በሃገሪቷ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 582 የደረሰ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ፤ 152 ሰዎች አገግመዋል።ሃገሪቷም እስካሁን ባለው 81 ሺህ 10 የላብራቶሪ ምርመራ አድርጋለች። የኮሮናቫይረስን ለመከላከል አካላዊ ርቀትን መጠበቅ፣ ጭምብል ማድረግ እንዲሁም በተደጋጋሚ እጃችንን መታጠብ በጤና ባለሙያዎች የሚሰጡ ምክሮች ናቸው። በተለይም በዛሬዋ ዕለት የኢድ አልፈጥር በዓልን ለምታከብሩ የእስልምና እምነት ተከታዮች ከቤተሰብ፣ ዘመድ፣ ወዳጅ ጋር አብሮ መቋደስ እንዲሁም መጠያየቅን ገታ በማድረግ ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ በዓሉ ይከበር።

የቀጥታ ሽፋን

  1. ብራዚል ሁለተኛዋ በርካታ የኮቪድ-19 በሽተኞች ያሉባት አገር ሆነች

    የቦልሶናሮ አገር ብራዚል በኮሮናቫይረሱ የተያዙ በርካታ ሰዎችን በመያዝ ከአሜሪካ በቀመጠል ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀመጠች።

    ብራዚል 330ሺህ 890 በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን የመዘገበች ሲሆን 21ሺህ 48 ሰዎች ደግሞ ከኮቪድ-19 ጋር በተያያዘ ህይወታቸውን አጥተዋል።

    በብራዚል ባለፉት 4 ቀናት በየዕለቱ የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ1ሺህ በላይ ነው።

    የጤና ባለሙያዎች አሁንም ቢሆን በብራዚል ለሰዎች የሚደረገው የኮሮናቫይረስ ምርመራ አነስተኛ ስለሆነ በቫይረሱ የሞቱ እና የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከዚህ በላይ ከፍ ያለ ሊሆን ይችላል ይላሉ።

    የዓለም ጤና ደርጅት ደቡብ አሜሪካ አዲሷ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ማዕከል ሲል ትናንት አስታውቆ ነበር።

    የብራዚሉ ፕሬዝደንት ጃይር ቦልሶናሮ የቫይረሱን ስርጭት ለመቆጣጠር በወሰዷቸው ደካማ እርምጃዎች በተደጋጋሚ ሲተቹ ነበር።

  2. ፈረንሳይ ሐይማኖታዊ አገልግሎቶች እንዲጀምሩ ፍቃድ ሰጠች

    ፈረንሳይ ሐይማኖታዊ አገልግሎቶች እንዲጀምሩ ፍቃድ ሰጠች።

    ሰዎች ወደ ማምለኪያ ስፍራዎች መጓዝ የሚጀምሩት ከሁለት ወራት በኋላ መሆኑ ነው።

    መንግሥት ይህን ክልከላ ሲያነሳ ሰዎች በማምለኪያ ስፍራዎች መከተል የሚጠበቅባቸውን ግዴታዎች ዘርዝሯል።

    የአገር ውስጥ ሚንስትሩ ሰዎች ወደ አምልኮ ስፍራ ከመግባታቸው በፊት እጆቻቸውን መታጠብ አለባቸው፣ የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ማድረግ አለባቸው እንዲሁም በሰዎች መካከል የሁለት ሜትር ርቀት መጠበቅ አለበት ብለዋል።

    የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ በተመሳሳይ መልኩ የአሜሪካ ግዛት አስተዳዳሪዎች የአምልኮ ስፍራዎችን መክፈት እንዲጀምሩ ጠይቀዋል።

    ትራምፕ የግዛት አስተዳዳሪዎች ይህን የማያደርጉ ከሆነ እርሳቸው የአምልኮ ሥፍራዎች እንዲከፈቱ ትዕዛዝ እሰጣለሁ ብለዋል። ምንም እንኳ ትራምፕ ይህን የማደረግ ስልጣን ባይኖራቸውም፤ ከፌደራል መንግሥቱ ለግዛቶች የሚሰጡ ድጋፎችን መከልከል ይችላሉ።

  3. ኮቪድ ያወጣቸው የቤተልሔም አበበ ገፀ ባህሪያት

  4. ቻይና ለመጀመሪያ ጊዜ በ24 ሰዓታት ውስጥ በቫይረሱ የተያዘ አላገኘችም

    ቻይና ለመጀመሪያ ጊዜ ወረርሽኙ ከጀመረ ወዲህ በግዛቷ በ24 ሰዓታት ውስጥ በቫይረሱ የተያዘ ሰው አለገኘሁም አለች።

    ይህም ብቻ ሳይሆን ብሔራዊ የጤና ኮሚሽን ባለፉት 24 ሰዓታት ከኮቪድ-19 ጋር በተያያዘ የሞተ ሰው አልተመዘገበም ብሏል።

    በቻይናዋ ዉሃን ከተማ ከ6 ወራት ገደማ በፊት ቫይረሱ ከተቀሰቀሰ ወዲህ በመላው ዓለም ተሰራጭቶ 5 ሚሊዮን ህዝብን አጥቅቷል። 338 ሺህ በላይ ሰዎችን ደግሞ ገድሏል።

    በቻይና ብቻ 84ሺህ ሰዎች በቫይረሱ የተያዙ ሲሆን 4600 ሰዎች ደግሞ ህይወታቸው አልፏል።

    የቻይና ባለስልጣናት ዉሃን ከተማን እና ዉቤይ ግዛትን እንቅቃሴ በመገደብ በቻይና ቫይረሱ በስፋት እንዳይሰራጭ ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል።

  5. ደቡብ አሜሪካ አዲሷ የኮሮናቫይረስ ስርጭት ማዕከል ሆናለች

    የዓለም ጤና ድርጅት ብራዚል በደቡብ አሜሪካ አዲሷ የኮሮናቫይረስ ስርጭት ማዕከል ሆናለች አለ።

    ድርጅቱ ትናንት ከደቡብ አሜሪካ አገራት ብራዚል ክፉኛ በቫይረሱ የተመታች አገር ናት ያለ ሲሆን፤ በአፍሪካም በቫይረሱ ምክንያት የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር አነስተኛ ቢሆንም በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ግን በፍጥነት እየጨመረ ነው ብሏል።

    በአፍሪካ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ከ100 ሺህ ማለፉ ሪፖርት ተደርጓል።

    ዛሬ [ቅዳሜ ጥዋት] አሃዞች እንደሚያሳዩት በአፍሪካ ባሉ አገራት በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 103 ሺህ 875 ደርሷል። 3ሺህ 184 የሚሆኑት ደግሞ ህይወታቸውን አጥተዋል።

    ደቡብ አፍሪካ ከ20ሺህ በላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን በመያዝ ቁጥር አንድ ስትሆን፤ ግብጽ፣ አልጄሪያ፣ ሞሮኮ እና ናይረጄሪያ ሌሎች ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች የሚገኙባቸው አገራት ናቸው።

    የዓለም ጤና ድርጅት ቫይረሱ በአፍሪካ ሪፖርት ከተደረገ ከ14 ሳምንት በኋላ በሁሉም የአህጉሪቱ አገራት ቫይረሱ መሰራጨቱን ባወጣው የጽሑፍ መግለጫ አስታውቋል።

    የድርጅቱ የአፍሪካ ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ማተሺዲሶ ማኦቲ የአፍሪካ አገራት የጤና ስርዓት ደካማ መሆኑን በማስታውስ የቫይረሱ ስርጭት በከፍተኛ ቁጥር ቢጨምር መቆጣጠር እንደሚዳግት አስጠንቅቀዋል።

    ከ50 በመቶ የሚሆኑት አገራት ደግሞ ባለፈው ሳምንት የ50 በመቶ ጭማሪ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች መዝግበዋል።

    የዓለም ጤና ድርጅት የአደጋ ጊዜ ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት ዶ/ር ማይክ ራይን በጋዜጣዊ መግለጫ ላይ፤ "ደቡብ አሜሪካ የቫይረሱ ስርጭት ማዕከል ሆናለች" ሲሉ መናገራቸውን ሬውተርስ ዘግቧል።

    ብራዚል ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባት አገር ናት። የአገሪቱ ባለስልጣናት የጸረ-ወባ መድሃኒት የሆነውን ሃይደሮክሎሪኪን ለኮቪድ-19 ተማሚዎችን እንዲሰጥ መወሰናቸውን ተናግረው፤ ይህ መድሃኒት የዚህ በሽታ ፈወሽ ስለመሆኑ ምንም ማረጋገጫ እንዳሌለው ዳግም አስታውሰዋል።

    ዶ/ር ማይክ ራይን ግማሽ በሚሆኑ የአፍሪካ አገራት ውስጥ ቫይረሱ በማህብረሰቡ ውስጥ እየተሰራጨ ነው ብለዋል።

    በአፍሪካ በቫይረሱ ምክንያት ብዙ ሰዎች ሊሞቱ ያልቻሉበት አንዱ ምክንያት ከጠቅላላው የአህጉሪቷ ህዝብ ገሚሱ 18 ዓመት እና ከዚያ በታች ስለሆኑ ሊሆን ይችላል ብለዋል።

  6. በጀርመን ሙስሊሞች ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንዲሰግዱ ተፈቀደላቸው

  7. የቦሪስ ጆንሰን አማካሪ ሥልጣን እንዲለቁ ግፊት እየተደረገባቸው ነው

    የዩናይትድ ኪንግደም ሕዝብ እንደራሴዎች የጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ዋና አማካሪ የእንቅስቃሴ ገደቡን መጣሳቸው ከተረጋገጠ ሥልጣናቸውን ይልቀቁ እያሉ ነው።

    ዋና አማካሪ ዶሚኒክ ካሚንግስ የኮቪድ-19 ምልክት እያለባቸው ከለንደን እስከ ደርሃም [400 ኪሎ ሜትር] ተጉዘዋል። ዶሚኒክ የበሽታ ምልክት እየታየባቸው ከነበሩት ባለቤታቸው ጋር በቤተሰቦቻቸው ቤት ራሳቸውን አግልለው ቆይተዋል።

    የሌበር ፓርቲ አባላት ቤተ-መንግሥቱ ዋና አማካሪው የፈፀሙትን ድርጊት እንዲያስረዳ እየጠየቁ ነው።

    የካሚንግ የቅርብ የሆኑ ሰው አማካሪው ምንም ዓይነት ሕግ አልጣሱም፤ ወደ ቤተሰቦቻቸው ቤት የሄዱት ልጆቻቸውን ለመርዳት ነው። ቢሆንም ራሳቸውን አግልለው ነው የቆዩት ይላሉ።

    የጠቅላይ ሚኒስትሩ መቀመጫ የሆነው ዳውኒንግ ስትሪት በጉዳዩ ላይ አስተያየት ከመስጠት ቢቆጠብም ዘግይቶ በወጣ መለግጫ አማካሪው ምንም ዓይነት ሕግ አልጣሱም ተብሏል።

    የለንደን ፖሊስም ሰውዬው ሕግ ባይጥሱም የበሽታ ምልክት እያለባቸው ይህን ሁሉ ኪሎሜትር ማቋረጣቸው ትክክል አይደለም ብሏል።

  8. ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች መድኃኒት ለማግኘት የሚያስችል ፍንጭ እየሰጡ ነው

  9. በጦርነት እየታመሰች ባለችው የመን የጤና ስርዓቷ እየወደቀ ነው

    በእርስ በእስር ጦርነት እየታመሰች ባለችው የመን የኮሮናቫይረስ ስርጭት እየጨመረ እና የጤና ስርዓቷ እየወደቀ ነው ሲል የተባበሩት መንግሥታት አስጠነቀቀ።

    የድርጅቱ ቃል አቀባይ ጉዳዩን "እጅግ አሳሳቢ" ሲሉ ገልጸውታል።

    ድርጅቱ እንደሚለው ከሆነ ሰዎች ወደ ጤና ተቋም ሲሄዱ ወደ መጡበት እንዲመለሱ ይደረጋል። ይህም የሆነበት ምክንያት የጤና ባለሙያዎች እራሳቸውን ከቫይረሱ ለመጠበቅ የሚለብሱት መከላከያ ቁሳቁሶች ስለሌላቸው ነው።

    ምንም እንኳ የየመን መንግሥት በቫይረሱ የሞቱ 30 ሰዎችን እና የተያዙ በርካታ ሰዎችን ሪፖርት ቢያደርግም፤ የተባበሩት መንግሥታት ግን አሃዙ መንግሥት ከሚለው እጅግ የላቀ ነው ይላል።

    በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ለመለየት የሚደረገው የኮሮናቫይረስ ምርመራ እጅግ አነስተኛ መሆኑም ተነግሯል።

    በሚሊዮን የሚቆጠሩ በጦርነት ውስጥ የቆዩት የመናውያን በምግብ እጥረት የተጎዱ ናቸው። ህይወታቸውም በእርዳታ ላይ የተመረኮዘ ሆኗል።

  10. የወባ መድኃኒት የኮቪድ-19 በሽተኞች ከማዳን ይልቅ ለሞት እየዳረገ ነው

  11. ደቡብ አፍሪካ ውስጥ በወረርሽኙ ምክንያት ወንጀል ቀነሰ

    በአፍሪካ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ከ100 ሺህ ማለፉ ተነግሯል።

    ዛሬ [ቅዳሜ ጥዋት] አሃዞች እንደሚያሳዩት በአፍሪካ ባሉ አገራት በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 103 ሺህ 875 ነው። 3ሺህ 184 የሚሆኑት ደግሞ ህይወታቸውን አጥተዋል።

    ደቡብ አፍሪካ ከ20ሺህ በላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን በመያዝ ቁጥር አንድ ስትሆን፤ ግብጽ፣ አልጄሪያ፣ ሞሮኮ እና ናይረጄሪያ ሌሎች ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች የሚገኙባቸው አገራት ናቸው።

    በቫይረሱ የተያዙ በርካታ ሰዎች የሚገኙባት ደቡብ አፍሪካ አሁንም በርካታ በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋጋጡ ሰዎችን መመዝገቧን ቀጥላለች። በቫይረሱ ከተያዙ መካከል ደግሞ 600 የሚሆኑት የፖሊስ አባላት መሆናቸውን የአገሪቱ ፖሊስ ሚንስትር ተናግረዋል።

    ደቡብ አፍሪካ ይህን ያክል በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ያገኘችው ወደ ግማሽ ሚሊዮን የሚጠጋ ህዝቧን ከመረመረች በኋላ ነው።

    አገሪቱ የቫይረሱን ስርጭት ለመቆጣጠር ጥብቅ የእንቅስቃሴ ገደብ መጣሏ ይታወሰል። አሁን እየወጡ ያሉ ሪፖርቶች እንደሚጠቁሙት ከሆነ፤ የእንቅስቃሴ ገደቦቹ የቫይረሱን ስርጭት ለመቀነስ ከመርዳታቸው በተጨማሪ፤ በአገሪቱ ይመዘገቡ የነበሩ የወንጀል መጠኖችን እንዲቀንስ አድርጓል።

    በእንቅስቃሴ ገደቡ ወቅት ሪፖርት ይደረግ የነበረው የአስገድዶ መድፈር ወንጀል በ84 በመቶ ቀንሷል። የግድያ ወንጀሎችም 64 በመቶ ቀንስዋል ተብሏል።

  12. በአፍሪካ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ከ100 ሺህ አለፈ

    በአፍሪካ አገራት በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ከ100 ሺህ አለፈ።

    አሁናዊ አሃዞች እንደሚያሳዩት በአፍሪካ ባሉ አገራት በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 103 ሺህ 875 ነው። 3ሺህ 184 የሚሆኑት ደግሞ ህይወታቸውን አጥተዋል።

    ደቡብ አፍሪካ ከ20ሺህ በላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን በመያዝ ቁጥር አንድ ስትሆን፤ ግብጽ፣ አልጄሪያ፣ ሞሮኮ እና ናይረጄሪያ ሌሎች ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች የሚገኙባቸው አገራት ናቸው።

  13. ኮሮናቫይረስ፡ አገራት የውጭ አገር ተጓዦችን እንዴት ይቀበላሉ?

  14. የታንዛኒያው ባለሥልጣን 'ኮሮናቫይረስ ጠፍቷል፤ ውጡና ጨፍሩ' እያሉ ነው

  15. ናይጄሪያዊያን ሃይድሮክሎሮኪን ለመግዛት እየተራወጡ ነው

  16. በምያንማር ዜና አርታኢው 'ትክክለኛ ባልሆነ' የኮቪድ-19 ሞት ዘገባ ታሰረ

  17. ጎንደር ውስጥ 4 ሰዎች ቫይረሱ ተገኘባቸው