የኬንያ ፓርላማ 50 እንደራሴዎቹ የኮሮና ምረመራ እንዲያደርጉ ጠየቀ

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
የኬንያ የታችኛው ምክር ቤት አባላት የሆኑ 50 እንደራሴዎች የኮሮናቫይረስ ምርመራ እንዲያደርጉ እንደሚፈልግ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤቱ ገለፀ።
ምክር ቤቱ ይህንን ሊል የቻለው በቅርቡ አንድ የሥራ ባልደረባቸው ቫይረሱ ስለተገኘባቸውና እነዚህ እንደራሴዎቹም በነበራቸው ንክኪ የተነሳ ለቫይረሱ ተጋላጭ ሊሆኑ ይችላሉ በሚል ነው።
ምክር ቤቱ የ50ውን የምክር ቤት አባላት ስም ዝርዝር ለጤና ሚኒስቴር ማስገባቱ ታውቋል።
አክሎም በአስገዳጅ ሁናቴ ለይቶ ማቆያ እንዲገቡ እንደሚፈልግ ገልጿል።
ከዚህ ቀደም በኮሮናቫይረስ የተያዙት የሕዝብ እንደራሴ ከጀርመን ከተመለሰ የኪሊፊ ምክትል አገረ ገዢ ጋር በነበራቸው ንክኪ በቫይረሱ መያዛቸው ታውቋል።
በኬንያ እስካሁን ድረስ 42 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ሲረጋገጥ ሁሉም አገሪቱም ድንበሯቿን በመዝጋት የሰዓት እላፊ ማወጇ ይታወሳል።












