በካሜሮን የሚገኙ ተገንጣይ ቡድኖች ሰዎች የኮሮናቫይረስ ምርመራ እንዲያደርጉ በሚል ለሁለት ሳምንት ያህል መሳሪያቸውን ለማስቀመጥ ተስማሙ።
የምዕራባዊ ካሜሮን መከላከያ ኃይል የሚባለው የአማፂ ቡድን እንዳለው የተኩስ አቁሙ ከእሁድ ጀምሮ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል፤ ይህንንም ”የመልካም ፈቃድ
ማሳያ” ብለውታል።
በካሜሮን በእርስ በእርስ ጦርነቱ ምከንያት ቀያቸውን ጥለው የተሰደዱ ዜጎች የኮቪድ-19 ምርመራ ማግኘት አይችሉም የሚል ስጋት ተፈጥሯል።
ካሜሮን ውስጥ እንግሊዘኛ ተናጋሪዎች ባሉበት አካባቢ ከሚንቀሳቀሱ በርካታ አማፂያን መካከል ይህ ቡድን ብቻ ነው የተኩስ አቁም ለማድረግ
የፈቀደው።
እነዚህ ተዋጊዎች በአብዛኛው ፈረንሳይኛ ተናጋሪ በሆነው አካባቢ ተገለናል ሲሉ ቅሬታ ያቀርባሉ።
ተገንጣይ ቡድኖቹ ለሦስት ዓመታት ከካሜሮን መንግሥት ጋር ሲዋጉ የነበረ ሲሆን ተገንጥለው የራሳቸውን “አምባዞኒያ” የተሰኘ ግዛት ለመመስረት ይፈልጋሉ።
እስካሁን አምባዞኒያ መከላከያ ኃይል የተሰኘውና ትልቁ የአማፂ ቡድን የተኩስ አቁም ያድርግ አያድርግ የታወቀ ነገር የለም።
በካሜሮን አማፂያኑን ወደ ውይይት እንዲመጡ የሚያግባባው ቡድን አባል የሆኑት አሌክሳንደር ሌቢስኪንድ ለቢቢሲ “ይህ ቡድን ብቻ ነው አሻፈረኝ ያለው” ሲሉ ተናግረዋል።
አክለውም በቅርቡ የተኩስ አቁሙን ይቀላቀላሉ ብለን ተስፋ እናደርጋለን ብለዋል።
ይህ የተኩስ አቁም ዓመታት የፈጀውን የካሜሮናዊያን ደም አፋሳሽ የእርስ በእርስ ጦርነት ያስቆመው እንደሆን የተባለ ነገር የለም።