በኤርትራ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ተጨማሪ 3 ሰዎች ተገኙ
ኤርትራ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ተጨማሪ ሶስት ሰዎች ማግኘቷን የኤርትራ ኢንፎርሜሽን ሚኒስቴር አስታውቋል።
ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ከዱባይ ባለፈው ቅዳሜ ወደ ኤርትራ የገቡ የኤርትራ ዜጎች መሆናቸው ታውቋል።
በዚህም መሰረት በኤርትራ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር አራት ደርሷል።
ቫይረሱ ከተገኘባቸው ሰዎች ጋር በተመሳሳይ አውሮፕላን የመጡና ንክኪ የነበራቸው ሰዎች በለይቶ ማቆያ ውስጥ እንዲገቡ ተደርገዋል።
ይህን ተከትሎም ከዛሬ ዕኩለ ሌሊት ጀምሮ ማንኛውም ወደ ኤርትራም ሆነ ከኤርትራ የሚደረጉ በረራዎች ለሁለት ሳምንታት እንዲቆሙ ይደረጋል ተብሏል።