ጀርመን በኬንያ የጠፋባትን 6 ሚሊዮን ማስክ እያፈላለገች ነው
የጀርመን ባለስልጣናት በኬንያ አየር ማረፊያ የጠፋውን 6 ሚሊዮን የፊት ማስክ እያፈላለጉ መሆኑ ተነገረ።
የጀርመን መንግሥት የፊት ማስኩን የህክምና ባለሙያዎቹ እንዲጠቀሙበት ከውጪ አገር በማዘዝ ወደ ጀርመን እያጓጓዛ ሳለ በኬንያ አየር ማረፊያ የገባበት አልታወቀም ተብሏል።
የጀርመኑ ዴር ስፒግል የተሰኘው ጋዜጣ የፊት ማስኩ ከአራት ቀናት በፊት ጀርመን መድረስ ነበረበት ሲል ዘግቧል።
የፊት ማስኩ ወደ ኬንያ አየር ማረፊያ እንዴት ሊመጣ እንደቻለ ግልጽ አልሆነም።
የጀርመን ጦር ቃል አቀባይ ለሬውተርስ "የሁለቱ አገራት ባለስልጣናት የተፈጠረውን ለመረዳት እየሞከሩ ነው" ሲሉ ተናግረዋል።
ሬውተርስ ጨምሮም የኬንያ ኤርፖርቶች ኃላፊ ጉዳዩን እያጣሩ ነው ሲል ዘግቧል።