ኬንያዊው ኮሮናቫይረስ አለብህ በሚል ጥርጣሬ ተደብድቦ ተገደለ
በሰሜን ምስራቅ ኬንያ ሰዎች ኮሮናቫይረስ ይዞታል ብለው የጠረጠሩትን አንድ ግለሰብ ደብድበው መግደላቸውን የአካባቢው ፖሊስ ለቢቢሲ አስታወቀ። የፖሊስ አዛዡ ነህሚያ ቢቶክ እንዳሉት እስካሁን በግለሰቡ ግድያ ተጠርጥሮ የተያዘ ሰው የሌለ ሲሆን ምርመራ ግን እየተካሄደ ነው።
ግድያው የተፈፀመው በኬንያዋ ክዋሌ ግዛት በአሳ ምርት በምትታወቀውና ምሳምብዌኒ በተባለች መንደር ነው። ቦታው በባህር ዳርቻውና በነጭ አሸዋው ውበት በቱሪስቶችም በእጅጉ የሚዘወተር ነው።