ሌበር ፓርቲ ስደተኞች በዩኬ ውስጥ ለመቆየት ለማኅበረሰቡ የሚያበረክቱትን አስተዋጽኦ ማረጋገጥ አለባቸው አለ

ታትሟል
የንባብ ጊዜ: 2 ደቂቃ

ስደተኞች በዩናይትድ ኪንግደም የመቆየት መብትን ለማግኘት ለኅብረተሰቡ አስተዋፅዖ እያደረጉ መሆናቸውን ማረጋገጥ አለባቸው ሲል የአገር ውስጥ ሚኒስትሯ አስታወቁ።

ሻባና ማህሙድ በሌበር ፓርቲ ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር ስደተኞች ላልተገደበ ጊዜ በዩናይትድ ኪንግደም የመቆየት ፈቃድ ለማግኘት ብቁ ለመሆን ማሟላት ያለባቸውን አዳዲስ መስፈርቶች ዘርዝረዋል።

በቀረበው ምክረ ሃሳብ መሠረት ሕጋዊ ስደተኞች እንግሊዘኛን በከፍተኛ ብቃት መማር፣ ምንም ዓይነት ወንጀል ውስጥ አለመሳተፍ እና ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ እንዲሰጣቸው በማኅበረሰቡ ውስጥ በበጎ ፈቃድ ማገልገል አለባቸው።

ሌበር ፖሊሲው በመንግሥት እና በሪፎርም ዩኬ መካከል ግልፅ የሆነ የልዩነት መስመር ያስቀመጠ ሲሆን ይህም ስደተኞች ላልተወሰነ ጊዜ የሚቆዩበትን ፈቃድ ማግኘትን ያስወግዳል ብሏል።

በአሁኑ ጊዜ ስደተኞች በዩኬ በቋሚነት የመኖር፣ የመማር እና የመስራት መብትን ለማግኘት ማመልከት የሚችሉት ከአምስት ዓመት በኋላ ነው።

ሌበር ፓርቲ ግን ይህንን ከአምስት ዓመት ወደ አስር ከፍ የማድረግ እቅድ አስቀምጧል።

ሪፎርም በበኩሉ ስደተኞችን፣ፈቃዱ ያላቸው እና የአውሮፓ ኅብረት ዜጎች ያልሆኑትን ጨምሮ በየአምስት ዓመቱ እንደገና በአገር ውስጥ ለመቆየት የሚያስችላቸውን ፈቃድ ለማግኘት እንዲያመለክቱ ለማድረግ አቅዷል።

ሌበር ይህ እቅድ ለዩናይትድ ኪንግደም ለአስርት ዓመታት አስተዋፅዖ ያደረጉ ሠራተኞች ቤታቸውን እና ቤተሰቦቻቸውን ለቅቀው እንዲወጡ ያስገድዳቸዋል ሲል ተችቶታል።

እሁድ ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ሰር ኬይር ስታርመር ከቢቢሲ ጋር በነበራቸው ቃለ መጠይቅ ላይ የሪፎርም ዩኬ ፖሊሲ "ዘረኛ" እና "ኢ ሞራላዊ" ነው ሲሉ ኮንነውታል።

የሪፎርም ዩኬ መሪ ኒጄል ፋራጅ ለዴይሊ ኤክስፕረስ እንደተናገሩት ሌበር "በድንበር ቁጥጥር አያምንም" ሲሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ አስተያየት "ተስፋ የቆረጠ አካል ጥቃት ነው" ብለዋል።

ሚኒስትሮች ስደተኞች በቋሚነት በዩናይትድ ኪንግደም መቆየት ከፈለጉ ከማኅበረሰቡ ጋር መቀላቀላቸውን እንዲያረጋግጡ ይፈልጋሉ።

ይህም እንደ የብሔራዊ መድን መዋጮችን መክፈል፣ ምንም ዓይነት የጥቅማ ጥቅም ድጎማ ክፍያ አለመውሰድ እና ማኅበረሰባቸውን ማገልገል የመሳሰሉ ሁኔታዎችን ማሟላትን ይጨምራል።

ሌበር ፓርቲ አንዳንድ የውጭ አገር ዜጎች ባደረጉት አስተዋፅዖ ወይም ባላቸው ክህሎት መሠረት ቀደም ሲል የአገር ውስጥ መቆያ ፈቃድን ሊያገኙ እንደሚችሉ ተናግሯል።

የፓርቲው ጉባዔ ዋነኛ አጀንዳ በአሁኑ ወቅት በዩኬ ከፍተኛ ተቀባይነት እያገኘ ያለውን ሪፎርም ዩኬን መገዳደር ነው።

ማህሙድ በንግግራቸው አገር ወዳድነት "ወደ ትንሽ ነገር እየተቀየረ ነው፣ ወደ ብሔር ብሔረተኝነትም እየተለወጠ ነው" ብለዋል።

ማህሙድ "ፍትሃዊ ስደት" እና አስተማማኝ ድንበሮች የ"ክፍት፣ ለጋስ፣ ታጋሽ" አገር ወሳኝ አካል ናቸው በማለት ይከራከራሉ።

ለፓርቲ አባላት "እኔ የማደርገውን ሁል ጊዜ አትወዱትም" ሲሉ ተናግረዋል።

አክለውም የሌበር መንግሥት ካልተሳካለት "ሠራተኛው መደብ ከእኛ ይርቃል" እና በኒጌል ፋራጌ ፓርቲ "ሐሰተኛ ተስፋዎች መጽናናትን ይፈልጋሉ" በማለት አስጠንቅቀዋል።

ማህሙድ ስለ ወላጆቻቸው ወደ ዩኬ መጥቶ የመምጣት ልምድ አውርተው፣ ስደተኞችን መቀበል ለአካባቢው ማኅበረሰብ በሚያበረክቱት አስተዋፅዖ ላይ የተመሰረተ ነው በማለት ይከራከራሉ።

ልጅ ሆነው በቤተሰቦቻቸው መደብር ውስጥ ሲሰሩ ዘራፊዎች እንዴት እንዳጠቋቸው በማንሳት ያም ወንጀልን ለመከላከል እንዳነሳሳቸው ተናግረዋል።

እሷ እንዴት የሱቅ ዝርፊያ ሰለባ እንደነበረች፣ በልጅነቷ ከቤተሰቧ የማዕዘን ሱቅ መደርደሪያ ጀርባ ስትሰራ እና ለምን ሌብነትን እንድትቆጣጠር እንዳነሳሳት ትናገራለች።

የአገር ውስጥ ሚኒስቴር ኃላፊዋ በንግድ አካባቢዎች የሚፈጸም ወንጀልን ለመቅረፍ የ"ክረምት የድርጊት መርሃ ግብር" በቅርቡ ይጀምራሉ።

ይህ በመላ አገሪቱ የሚገኙ የፖሊስ ባልደረቦች ከአካባቢው የንግድ ተቋማት ጋር በመተባበር መሥራትን ይጨምራል።