በዲሞክራቲክ ኮንጎ 16 ተሳፋሪዎች የጫነ አውሮፕላን መኖሪያ ቤቶች ላይ ተከሰከሰ

የተከሰከሰው አውሮፕላን

የፎቶው ባለመብት, @eliezaireushin

ታትሟል

አስራ ስድስት ተሳፋሪዎችን እና ሁለት የአውሮፕላን ሰራተኞችን አሳፍሮ የነበረው አውሮፕላን ጎማ ከተማ መኖሪያ ቤቶች ላይ መከስከሱን የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ሰሜናዊ ክልል ኪቩ ገዥ ናዛናዙ ካሲቪታ አስታውቀዋል።

በመነሳት ላይ ሳለ ችግር የገጠመው ይህ አውሮፕላን በአንድ ደቂቃ ውስጥ የተከሰከሰው በጎማ ከተማ ማፔንዶ በተሰኘ ሰፈር መኖሪያ ቤቶች ላይ ነው።

በአውሮፕላኑ አደጋ ሰዎች መሞታቸውን የተናገሩት ገዥው ምን ያህል ሰዎች ለሚለው ግን ቁጥር አላስቀመጡም።

አውሮፕላኑ ቢዚ ቢ የተባለ የግል አየር መንገድ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።

አውሮፕላኑ ከጎማ ከተማ የተነሳው ወደ ቤኒን ለማቅናት ነበር።

የአቪዬሽን ደህንነት ቁጥጥር የላላ ነው በሚባልባት በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የአውሮፕላን አደጋ ይደጋገማል። አውሮፕላን ጥገና ችግርም ለተደጋጋሚ አደጋዎች በምክንያትነት ይቀመጣል።

የአገሪቱ ሁሉም የግል አየር መንገዶች በአውሮፓ እንዳይንቀሳቀሱ በአውሮፓ ህብረት ዕግድ ተጥሎባቸዋል።