የትራምፕ ልዑክ ከሐማስ አመራሮች ጋር ከተገናኙ በኋላ ከኔታንያሁ ጋር ተወያዩ

የፎቶው ባለመብት, AFP via Getty Images
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የመካከለኛው ምሥራቅ ልዑክ ጃሬድ ኩሽነር ከእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሀ ጋር መገናኘታቸውን ቃል አቀባዩ ለቢቢሲ ተናገሩ።
ኩሽነር እስራኤል የደረሱት ከሐማስ ጋር ከተነጋገሩ በኋላ ትናንት ምሽት ነው።
የትራምፕ የሰላም ቦርድ ባለፈው ወር በጋዛ ውስጥ ሐማስን እና ሌሎች የታጠቁ ቡድኖችን "ሙሉ በሙሉ ትጥቅ ለማስፈታት" ስምምነት ላይ ከደረሰ በኋላ እስራኤል ባለ 15 ነጥቡን የሰላም ዕቅድ ውድቅ አድርጋለች።
የሰላም ዕቅዱ የእስራኤል ወታደሮች እንዲወጡ እና ጋዛ በአዲስ የሲቪል አስተዳደር ስር ዳግም እንድትገነባ ይጠይቃል።
ስምንት ሙስሊም አገራት ትናንት እሁድ ባወጡት መግለጫ እስራኤል ዕቅዱን ውድቅ ማድረጓን ኮንነዋል።
ትራምፕ በጋዛ ሰላም ለማስፈን ታስቦ የተቋቋመውን የሰላም ቦርድን የሚመሩ ሲሆን፣ በኋላ ላይ በዓለም ዙሪያ የሚከሰቱ ግጭቶችን መፍታት እንደሚያካትት ተገልጿል።
እሁድ ዕለት አንድ የፍልስጤም ባለሥልጣን ለቢቢሲ እንደተናገሩት የትራምፕ ልዑክ በግብፅ የሐማስ አዲሱ መሪ ካሊል አል-ሃይያ የሚመራውን ልዑክ አግኝተው ነበር።
ሃማስ ባወጣው መግለጫ፣ በኋላ ላይ አስታራቂዎችን እና የሰላም ቦርዱን እስራኤል ለቀጣዮቹ እርምጃዎች የመንገድ ካርታውን እንድታፀድቅ "እንዲያስገድዱ" ጥሪ አቅርቧል።
ሐማስ በኋላ ላይ ባወጣው መግለጫ አደራዳሪዎች እና የሰላም ቦርዱ እስራኤል ለቀጣዩ እርምጃ ፍኖተ ካርታውን እንድታጸድቅ “እንዲያስገድዱ” ጠይቋል።
ብዙ እስራኤላውያንም ሐማስ ትጥቅ ለመፍታት ዝግጁ መሆኑ ላይ ጥርጣሬ አላቸው።
ኩሽነር ከሃይያ ጋር ያደረጉት ስብሰባ ባለፈው ዓመት በጋዛ ሰርጥ የተኩስ አቁም እንዲኖር ከተደረገው ስምምነት ወዲህ የመጀመሪያው እንደሆነ ይታመናል።





