በአሜሪካ አሸማይነት ለበርካታ ቀናት ዋሽንግተን ድርድር ሲያካሂዱት የነበሩት እስራኤል እና ሊባኖስ፤ የስምምነት ማዕቀፍ ላይ ተፈራረሙ።
የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ
እንደገለጹት አሁን በተፈረመው ስምምነት አማካኝነት ዘላቂ ሰላም እና ደኅንነትን ለማስፈን የሚያስችል ማዕቀፍ መዘጋጀት ይጀምራል።
ሁለቱ አገራት መፈራረማቸው የተሰማው፤ በእስራኤል
ኃይሎች እና በኢራን በሚደገፈው ሄዝቦላህ ተግባራዊ እየሆነ ያለው ተኩስ አቁምን ወደ ጎን በማለት ደቡብ ሊባኖስ ውስጥ የተወሰነ
ውጊያ ማድረግ በቀጠሉበት ወቅት ነው።
የእስራኤል ጋር እየተዋጋ ያለው ሄዝቦላህ አርብ
ዕለት የተፈረመው ስምምነት አካል አይደለም። ቡድኑ በስምምነቱ አማካኝነት በደቡብ ሊባኖስ ከሚገኘው ደቡብ ሊታኒ አካበቢ ለማስወጣት
ይስማማ እንደሆን ግልጽ አይደለም።
አሜሪካ፤ በእስራኤል እና ሄዝቦላ መከካል ያለው
ውጥረት ከኢራን ጋር የተደረገውን የሰላም ስምምነት ሊያደናቅፍ ይችላል የሚል ስጋት ገብቷታል።
ከአሜሪካ ጋር በተፈረመው ስምምነት
ላይ ኢራን ሊባኖስን ጨምሮ "በሁሉም ግንባሮች" ውጊያ እንዲቆም ያቀረበችው ጥያቄ ተግባራዊ እንደሚሆን ቃል
ተገብቶላታል።
እስራኤል እና ሊባኖስ በተፈራረሙት ባለ 14
ነጥብ የማዕቀፍ ስምምነት ላይ አንዳቸው ሌላኛቸው "በሰላም የመኖር" መብት እንዳለው "ማረጋገጫ"
ሰጥተዋል። "እንደ ተጎራባች ሉዓላዊ አገራት በደኅንነት ለመኖር ያላቸውን የጋራ ፍላጎትም" ገልጸዋል።
ሁለቱ አገራት "በዓለም አቀፍ የፖለቲካ
ወይም የሕግ መድረኮች ላይ የሚደረጉ ማናቸውንም ጠበኛ ወይም የጠላትነት ድርጊቶች ለማቆምም" ተስማምተዋል። እስረኞችን ለመልቀቅ እና የሞቱ ሰዎችን ማንኛውም ቅሪት አሳልፎ ለመስጠትም
ቃል ገብተዋል።
ይሁን እንጁ ሁለቱም መንግሥታት የተፈረመው “ማዕቀፍ
ራሳቸውን የመከላከል ተፈጥሯዊ መብታቸውን ከመጠቀም እንደማያግዳቸው" ዕውቅና ሰጥተዋል።
ስምምነቱ እንደሚገልጸው "መንግሥታዊ
ያልሆኑ ታጣቂ ቡድኖች ትጥቅ መፍታታቸው እና ተያያዥ መሠረተ ልማቶች መፍረሳቸው እስኪረጋገጥ ድረስ" የሊባኖስ ጦር ኃይሎች
በሁሉም የሊባኖስ ግዛቶች ውስጥ ሉዓላዊ ሥልጣን ይኖራቸዋል።
ይህንን ዕቅድ ለማሳካት ሲባል ሊባኖስ “በአሜሪካ
መሪነት” የዓለም አቀፍ እና “በተለይም የአረብ አጋሮችን” ድጋፍ ትጠይቃለች።
ማዕቀፉን ለማስፈጸም እንዲቻልም በአሜሪካ የሚደገፍ
ወታደራዊ የቅንጅት ቡድን እንደሚቋቋምም ተገልጿል።