ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዐቢይ አሕመድን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አድርጎ ሾመ።
ምክር ቤቱ ሹመቱን ያጸደቀው ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በብልጽግና ፓርቲ ለጠቅላይ ሚኒስትርነት ቦታ ዕጩ አድርጎ ካቀረባቸው በኋላ ነው።
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከፍተኛውን የሕግ አስፈጻሚ አካል ስልጣን ለቀጣይ አምስት ዓመታት ይይዛሉ።
በዚህ መሠረት ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ የአገሪቱ መስተዳድር መሪ፣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሰብሳቢ እና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ይሆናሉ።
ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልጣን ተግባራት መካከል የሚመርጧቸውን የሚኒስትሮች ምከር ቤት አባላትንና ሌሎች ላላፊዎችን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርበው እንዲሾሙ ያደርጋሉ።