በበርካታ የአሜሪካ ግዛቶች ኮሮናቫይረስ ዳግም እየተሰራጨ ነው
ትናንት የወጡ አሃዞች እንዳመላከቱት በበርካታ የአሜሪካ ግዛቶች ውስጥ ኮሮናቫይረስ ዳግም እየተሰራጨ ነው።
በደቡብ እና ምዕራብ አሜሪካ በሚገኙ ግዛቶች ደግሞ ስርጭቱ አይሎ ታይቷል። ከጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ የተገኘው አሃዝ እንደሚያመላክተው በ16 ግዛቶች በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ነው።
አሪዞና፣ አላባማ፣ ዋሽንግተን፣ ሳውዝ ካሮላይና፣ ዩታህ፣ ቴክሳስ፣ ሚሲሲፒ፣ ፍሎሪዳ እና ጆርጂያ ቫይረሱ እየተሰራጨባቸው ይገኛል ከተባሉት ግዛቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው።
በአሪዞና የሚገኙ ሆስፒታሎች እስከ አቅማቸው ጫፍ ድረስ ታማሚዎች እየተቀበሉ ነው።
እስካሁን ድረስ በአሜሪካ 119ሺህ ገደማ ሰዎች በኮቪድ-19 ምክንያት ህይወታቸውን አጥተዋል።