በምስራቅ አፍሪካዋ አገር ታንዛንያ የኮሮናቫይረስ ስርጭት ቀንሷል ተባለ
የታንዛንያ ጤና ሚኒስትር በአገሪቱ ያለው የኮሮናቫይረስ ስርጭት መቀነሱን ጠቅሰው የንግድ ከተማ በሆነችው ዳሬ ሰላም አራት በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ብቻ መኖራቸውን ገለፁ።
ኡሚ ምዋሊሙ አክለውም በታንጋ እና ምዋንዛ ግዛቶች ምንም በቫይረሱ የተያዘ ሰው አለመኖሩን ተናግረዋል።
የታንዛንያ መንግሥት ፕሬዝዳንት ማጉፉሊ ባለስልጣናት ቁጥር ያጋንናሉ ብለው ከተናገሩ በኋላ ከሚያዚያ ወር ጀምሮ የአገሪቱን የኮሮናቨይረስ እለታዊ መረጃ ይፋ ማድረግ አቁሟል።
ባለፈው ወር የአሜሪካ አምባሳደር በዳሬ ሰላም የሚገኙ ሆስፒታሎች በህሙማን ተጥለቅለቀዋል በማለት በከተማዋ በኮሮናቫይረስ የመያዝ እድል ሰፊ መሆኑን ተናግረው ነበር።
የጤና ሚኒስትሩ ምዋሊሙ ሰኞ እለት ለተሰበሰቡ ጋዜጠኞች ፈጣሪ ታንዛንያን ታድጓል ሲሉ ተናግረዋል።
የታንዛንያ መንግሥት ከሰኞ ዕለት ጀምሮ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመጨረሻ ዓመት ተማሪዎች ትምህርታቸውን እንዲጀምሩ ካስታወቀ በኋላ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው ተመልሰዋል።