አንድ ሺህ የሚጠጉ አፍሪካዊያን የጤና ባለሙያዎች በቫይረሱ ተይዘዋል ተባለ

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
የአለም ጤና ድርጅት በትዊተር ገፁ እንዳሰፈረው በአፍሪካ ውስጥ ወደ አንድ ሺህ የሚጠጉ የጤና ባለሙያዎች በኮሮናቫይረስ ተይዘዋል ብሏል።
ድርጅቱ በተጨማሪም የአፍሪካ መንግሥታት ለነርሶችና ዶክተሮች የመከላከያ ቁሳቁሶች እንዲያሟሉ ጥሪ አቅርቧል።
ከኮሮና ህሙማን ጋር ንክኪ የሚኖራቸው የህክምና ባለሙያዎች ራሳቸውን የሚከላከሉበት የህክምና ቁሳቁሶችን መሟላታቸውን መንግሥታት እርግጠኛ መሆን አንዳለባቸውም አፅንኦት ሰጥቷል።
በተለይም ከህሙማኑ ምራቅ ናሙና ጋር ንክኪ ያላቸው የላብራቶሪ ሰራተኞችም ሆኑ ዶክተሮች ደረጃውን የጠበቀ መከላከያ ያስፈልጋቸዋልም ተብሏል። ከዚህም ውስጥ በውስጡ መተንፈሻ የተገጠመለት ፊታቸውን ሙሉ በሙሉ የሚሸፍን ጭምብልና ቶሎ ቶሎ መቀየር የሚችሉ ጋወኖች ይገኙበታል ።
ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።
የ X ይዘት መጨረሻ














