ሕንድ በስልክ ጥሪ ስለኮሮናቫይረስ መረጃ እየሰጠች ነው
በሕንድ የሚገኙ በርካታ የሞባይል ኔትወርክ አቅራቢዎች ደንበኞቻቸው ማንኛውንም ጥሪ ከማድረጋቸው በፊት ለ30 ሰከንድ የኮሮናቫይረስ መረጃ እንዲያገኙ እያደረጉ ነው።
ጂሎ፣ ቢኤስኤንኤል እና ቮዳፎን የተባሉት ኩባንያዎች መንግሥት ያቀረበላቸውን ጥያቄ ተቀብለው ተግባራዊ ካደረጉት መካከል ይገኙበታል።
መልዕክቱ በእንግሊዘኛ የሚሰራጭ ሲሆን ማንኛውም ሰው ሲደውል ከጥሪው በፊት የሚያስል ሰውና የጤና መልዕክቱን ይሰማሉ።
ነገር ግን አንዳንድ ደንበኞች በመልዕክቱ መበሳጨታቸውን ደጋግመው በመግለጻቸው የተነሳ በርካታ ድረ-ገጾች መልዕክቱን እንዴት ማስቆም እንደሚቻል የሚገልፅ መረጃ እያሰራጩ ይገኛሉ።