በአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶችና ሲኒማ ቤቶች ዝግ ሆነው ይቆያሉ ተባለ, በአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶችና ሲኒማ ቤቶች ዝግ ሆነው ይቆያሉ ተባለ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኙ አራት ቴአትር ቤቶች እና የመንግሥት ሲኒማ ቤቶች ከትናንት ጀምሮ ለ15 ቀናት ለሕዝብ አገልግሎት ዝግ መሆናቸው ተነገረ።
ትዕዛዙ የተላለፈው ትናንት ሲሆን ይህንን ተከትሎም ሁሉም ትያትር ቤቶችና ሲኒማ ቤቶች ዝግ መሆናቸው ይታወቃል።
በትናንትናው እለት ሴንቸሪ ሲኒማ ለተጠቃሚዎቹ በቴሌግራም ገፁ ላይ ባስተላለፈው መልዕክትም ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ ለቀጣይ 15 ቀናት ዝግ እንደሚሆን አስታውቋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ በትናንትናው ዕለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችና ትልልቅ ስብሰባዎች ለቀጣዮቹ 15 ቀናት እንደሚዘጉ አስታውቀዋል።
በኢትዮጵያ እስካሁን ድረስ አምስት ሰዎች ቫይረሱ ተገኝቶባቸው በለይቶ ማቆያ ውስጥ እንደሚገኙ ይታወቃል።