የዓለም ጤና ድርጅት ኮቪድ-19ን በቁጥጥር ስር ለማዋል አገራት
በበሽታው የሚጠረጥሯቸውን ግለሰቦች በሙሉ እንዲመረምሩ አሳሰበ።
በአሁኑ ወቅት ሁሉም የአፍሪካ አገራት ቫይረሱን የማይመረምሩ ሲሆን ይህ ደግሞ በአህጉሪቱ የህሙማንን ቁጥር ከፍ ያደርጋል
ተብሎ ተሰግቷል።
እስካሁን 30 ያህል የአፍሪካ አገራት በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች ማግኘታቸውን የገለፁ ሲሆን አብዛኞቹ አነስተኛ ቁጥር
ያላቸው ሕሙማንን ብቻ ነው የመዘገቡት።
ይህ ቢሆንም እንኳ እንደ ጉዞ እገዳ ያሉ እርምጃዎችን የወሰዱ አገራት አሉ።
አሁንም ቢሆን ግን በርካታ አፍሪካ አገራት የኮሮናቫይረስን ለመመርመር የሚያስችል አቅሙ የላቸውም ተብሏል።
ሶማሊያ በሽታውን ለመቆጣጠር ዓለም አቀፍ በረራዎችን ማገዷን በትናንትናው ዕለት አስታውቃለች።
ሱዳን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ያወጀች ሲሆን አገር አቀፍ የመንቀሳቀስ እገዳ አስቀምጣለች።
ከኮሮናቫይረስ ጋር በተያያዘ በአፍሪካ ያለውን ሁኔታ ለመከታተል የተቋቋመው አፍሪካ ሲዲሲ ወረርሽኙን ለመቆጣጠር በፍጥነት
ምርመራ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ይመክራል።
ቻይናዊው ቢሊየነር ጃክማ ከአንድ ሚሊየን በላይ መመርመሪያዎችን፣ ስድስት ሚሊየን አፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብሎችንና የመከላከያ አልባሳት ለመለገስ ቃል መግባቱ ይታወሳል።