ይህ ዝቅተኛ ዳታን በመጠቀም ጽሑፍ ብቻ የሚቀርብበት የቢቢሲ አማርኛ ድረ ገጽ ነው
የልጁን ህይወት ለማትረፍ ናይል ወንዝ የገባው አባት አስከሬኑ ተገኘ
የልጁን ህይወት ለማትረፍ ናይል ወንዝ የገባው አባት አስከሬኑ ተገኘ።
የ48 አመቱ ሮበርት ክዌሲ የልጁን ህይወት ለመታደግ ናይል ወንዝ ከገባ በኋላ ለቀናት ጠፍቶ የነበረ ሲሆን በኋላም በነፍስ አድን ሰራተኞች አስከሬኑ ተገኝቷል።
ሮበርት የልጁን ህይወት ማትረፍ ቢችልም እሱ ግን ይህችን አለም ተሰናብቷል።
በእንግሊዝ ነዋሪ የነበረው ሮበርት ከባለቤቱ ጀስቲን ካታንታዚ እና ከአራት ልጆቻቸው ጋር ኡጋንዳ የመጡት ለእረፍት ነበር።
የ12 አመት ልጁም እየዋኘ በነበረበት ወቅት በነበረው ማዕበል ችግር ስላጋጠመው አባትየው ልጁን ለመርዳት ዘሎ ገና። ልጁን ቢያተርፍም ሮበርት ግን ደብዛው ጠፋ።
ጠላቂ ፖሊሶች እና የአካባቢው በጎ ፈቃደኞች ከያዝነው ሳምንት ረቡዕ ጀምሮ ሮበርትን እየፈለጉ ነበር። ከቀናት ፍለጋ በኋላም በናይል ወንዝ በአንደኛው ክፍል አስከሬኑ ተገኝቷል።
ባለቤቱ ጀስቲን ሮበርት ልጃቸውን ለማዳን ወደ ወንዙ ከገባ በኋላ እንደጠፋ አስረድታለች።
የኡጋንዳ ተወላጅና የእንግሊዝ ዜግነት ያለው ሮበርት ፍሪጅ እና አየር ማቀዝቀዣዎችን በመጠገን በተቋራጭነት ይሰራ ነበር።
የ12 ዓመት ልጃቸው ባረፉበት ፓክዋጅ ሎክ አቅራቢያ ባለው ናይል ወንዝ እየዋኘ በነበረበት ወቅት ከከፍተኛ ማዕበል ጋር እየታገለ ነበር።
ሮበርት እና ጀስቲን ጋብቻቸውን የፈጸሙት ከጥቂት ሳምንታት በኡጋንዳ ሲሆን ባለቤቷንም ደስተኛ እና የቅርብ ጓደኛዬ ነበር ስትል ገልጻዋለች።
የዩናይትድ ኪንግደም የውጭ፣ የኮመንዌልዝ እና ልማት ጽህፈት ቤት ቃለ አቀባይ ቤተሰቡን እየረዳ መሆኑን እና ከአካባቢው ባለስልጣናት ጋር በቅርበት እየተነጋገሩ መሆኑን ተናግረዋል።