ኮሮናቫይረስ፡ ኮቪድ-19 በሁለተኛው ዙር የከፋ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል- ተመራማሪዎች
ታትሟል
ብዙ አገራት በኮሮናቫይረስ በመጀመሪያ ዙር ክፉኛ ተጠቅተው መቆጣጠር ቢችሉም ወረርሽኙ ድጋሚ አገርሽቶ እየፈተናቸው ነው። ከዚህ ቀደም ተከስተው የነበሩ ወረርሽኞች ተሞክሮ እንደሚያሳየው በድጋሚ ሊያገረሽ ይችላል። ከ100 ዓመት በፊት ተከስቶ ቢያንስ 50 ሚሊዮን ህዝብ እንደጨረሰ የሚነገርለት ስፓኒሽ ፍሉ፣ ከመጀመሪያውም ሆነ ከሦስተኛው ጊዜ በላይ ሁለተኛው ዙር የከፋ ጉዳት አድርሷል። የኮሮናቫይረስም ተመሳሳይ ሂደት ሊከተል እንደሚችል ሳይንቲስቶች እያስጠነቀቁ ነው።