በዓለም ዙሪያ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 600 ሺህ ደረሰ
በዓለም ዙሪያ በኮሮናቫይረስ ስለተያዙ ሰዎች አዲስ አዲስ የወጣ መረጃ እንዳመለከተው አሁን ቁጥሩ ከ600 ሺህ ማለፉን ተነገረ።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በአውሮፓ በወረርሽኙ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ20 ሺህ ማለፉን በበሽታው ዙሪያ ያለውን መረጃ እየተከታተለ የሚያቀርበው የጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቨርስቲ አመልክቷል።
አሁን በበሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥር በአንድ መቶ ሺህ የጨመረው አሃዙ ግማሽ ሚሊዮን መድረሱ ከተነገረ በሁለት ቀናት ውስጥ ነው።
በመላው ዓለም በወረርሽኙ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 100 ሺህ የደረሰው የካቲት 27፣ 200 ሺህ የገባው መጋቢት 09፣ 300 ሺህ የደረሰው መጋቢት 12 እንዲሁም 400 ሺህ የሆነው ደግሞ መጋቢት 15/2012 ዓ.ም እንደሆነ የጆንስ ሆፕኪንስ መረጃ አመልክቷል።
ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰው በበሽታውየተያዘባቸው አገራት፡
• አሜሪካ 104,865ሰዎች
• ጣሊያን 86,498ሰዎች
• ቻይና 81,996ሰዎች
• ስፔን 72,248ሰዎች
• ጀርመን 53,340ሰዎች