ለ28 ዓመታት በባቱ ሐይቅ ገሊላ ደሴት ብቻቸውን የኖሩት አዛውንት

ለ28 ዓመታት በባቱ ሐይቅ ገሊላ ደሴት ብቻቸውን የኖሩት አዛውንት
ታትሟል

ወ/ሮ ኩሼ ጎንዶር ትዳር የመሰረቱት በ15 ዓመታቸው በባቱ ሐይቅ ገሊላ ደሴት ነው። ሦስት ልጆች ወልደዋል። ልጆቻቸው አካባቢውን ለቅቀው ሌላ ቦታ መኖር ጀምረዋል።

ጎረቤቶቻቸውም ከደሴቲቱ ወጥተው ከተማ ቢገቡም ወ/ሮ ኩሼ ግን ከደሴቷ አልወጣም ብለው ብቻቸውን እየኖሩ ነው።

ጎረቤቶቻቸውም ልጆቻቸውም በሌሉበት ያለፉትን 28 ዓመታት ወ/ሮ ኩሼ በደሴቷ ብቻቸውን አሳልፈዋል።

ወደፊትም ከደሴቷ የመውጣት እቅድ የላቸውም።